የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገለፁ

By Feven Bishaw

May 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መበራከቱን ተከትሎ ምርመራው በስፋት እየተካሄደ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በአዲስ አበባ በኅብረተሰቡ ውስጥ መሰራጨቱ በመረጋገጡ የምርመራ አድማሱን በማስፋት በተለይም በሥራቸው ባህሪይ ለቫይረሱ ተጋላጭ የሆኑ የኀብረተሰብ ክፍሎች ላይ ምርመራው ተጠናክሯል።