የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ሕሙማንን ለሚያክሙ 1 ሺህ 750 የጤና ባለሞያዎች ጊዜያዊ መኖሪያ ቤቶች ተዘጋጀ

By Tibebu Kebede

May 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ሕሙማንን እያገለገሉ ለሚገኙ 1 ሺህ 750 የጤና ባለሙያዎች ጊዜያዊ መኖሪያ ቤቶች መዘጋጀታቸውን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደስ ገልጸዋል።

የኮቪድ ሕሙማንን የሚያክሙ የጤና ባለሞያዎች ራሳቸውን ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳያደርጉ የኢንፌክሽን መከላከያ ቁሳቁስ በማቅረብ ረገድ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።