አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለከተማ ግብርናና ለችግኝ ተከላ መርሀግብር እየተደረጉ ያሉ ዝግጅቶችን በተመለከተ ውይይት ተደረጓል።
በተያዘው አመት በከተማ ደረጃ ለታቀደው 7 ሚሊየን ችግኝ የመትከል እቅድ የመሬት ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን የችግኝ ዝግጅቶችም እየተደረጉ ይገኛሉ። የችግኝ ዝግጅቱ በአስተዳደሩና በተደራጁ ወጣቶች የተደረገ መሆኑን ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።