አዲስ አበባ፣ ግንቦት24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በሶማሌ ክልል በ2011 እና 2012 የበጀት ዓመታት 53 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶችን በመቆፈርና በጥራት በመገንባት ለክልሉ አርብቶ – አደር ሕብረተሰብ ጥቅም እንዲውሉ መደረጉን የክልሉ የውሃ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ አዲሱ የለውጥ መንግስት ወደ ሃላፊነት ከመጣ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ የስርዓት ሽግግር ከመዘርጋት ስራ ጎን ለጎን የተለያዩ የልማት ስራዎችን ሲተገብር መቆየቱን የሶማሊ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ አስታውቋል።