Fana: At a Speed of Life!

የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የ2016 ምርት ዘመን ስኳር የማምረት ሥራውን የሸንኮራ አገዳ በመፍጨት ጀምሯል፡፡

በዚህ ዓመት በ4 ሺህ 600 ነጥብ 5 ሄክታር ላይ የለማ የሸንኮራ አገዳን በግብዓትነት በመጠቀም 245 ሺህ 927 ነጥብ 5 ኩንታል ስኳር ለማምረት አቅዶ ወደ ሥራ መግባቱም ተገልጿል፡፡

የፋብሪካው አጠቃላይ የክረምት ጥገና ተከናውኖ ታኅሣስ 26 ቀን 2016ዓ.ም ቦይለር መለኮሱን ከኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.