Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 5 ሺህ 369 የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ተገነቡ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ 5 ሺህ 369 የመምህራን መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸውን የክልሉ ትምህር ቢሮ አስታውቋል፡፡

በቢሮው የእቅድ ዝግጅትና ክትትል ግምገማ ዳይሬክተር አቶ ሀሰን እድሪስ እንዳሉት፥ በ2016 በጀት ዓመት በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

በዚህም ለመማር ማስተማር ሒደቱ እና ለትምህርት ጥራት አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በጥናት የመለየት ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡

በተለይም የመማር ማስተማር ሒደቱ የጀርባ አጥንት ለሆኑት መምህራን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ተሰርቷል ብለዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራትም ከ4 ሺህ 500 በላይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ 5 ሺህ 369 ቤቶችን በመገንባት ከዕቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን ነው የገለጹት፡፡

በቀጣይ ለመምህራን ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እና በትምህርት ጥራት ላይ የሚኖራቸውን ሚና ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.