የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚዬምን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚዬምን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ በትናንትናው ዕለት መካሄድ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በስብሰባው በዐበይት ሀገራዊ ጉዳዮች እና ልዩ ልዩ የፓርቲ አጀንዳዎች ላይ እንደሚመክር ተመላክቷል፡፡