Fana: At a Speed of Life!

ከ630 ሜትሪክ ቶን በላይ ከደረጃ በታች የሆነ ምርት ወደ ሀገር እንዳይገባ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠናቀቀው ግማሽ ዓመት ከ630 ሜትሪክ ቶን በላይ ምርቶች ከደረጃ በታች በመሆናቸው ምክንያት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ማድረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የ5 ሺህ 713 አስመጪዎችን ጥያቄ በመቀበል ከ1 ሚሊየን 868 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው የገቢ ዕቃዎች ላይ የጥራት ቁጥጥር ሥራ ማከናወኑንም ነው ሚኒስቴሩ የገለጸው፡፡

በዚህም 630 ነጥብ 21 ቶን የተለያየ የምግብ ውጤት፣ የኮንስትራክሽንና የኬሚካል ውጤት ላይ በተደረገ የላቦራቶሪ ፍተሻ እና የኢንስፔክሽን ሥራ ከደረጃ በታች መሆናቸው ተረጋግጦ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ታግደዋል ነው የተባለው፡፡

በቀጣይም የጥራት ማረጋገጥ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.