አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ ተመስገን ጥሩነህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል፡፡
የብልጽግና ማዕከላዊ ኮሚቴ የፓርቲውን የአመራር የመተካካት መርህንና የአሰራር ሥርዓት በመከተል ዛሬ ባካሄደው የማጠቃለያ ስብሰባ በሙሉ ድምፅ አቶ ደመቀ መኮንን በክብር ሸኝቷል፡፡
በምትካቸውም የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ የነበሩትን አቶ ተመስገን ጥሩነህን ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ በአብላጫ ድምጽ መርጧል።