አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ ወደ ቡድን 7 አባል ሀገራት ዳግም ተመልሳ እንድትቀላቀል ያቀረቡትን ጥሪ የአባል ሀገራቱ መሪዎች ውድቅ ማድረጋቸው ተሰምቷል።
በአሜሪካ አዘጋጅነት በያዝነው ወር እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የቡድን 7 ሀገራት ጉባዔ እስከ ፊታችን መስከረም ወር ሊራዘም እንደሚችል ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ቅዳሜ አስታውቀዋል።