Fana: At a Speed of Life!

የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ስልጠና ለገቡ ሰልጣኞች አቀባበል ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ስልጠና ለገቡ ሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጓል፡፡

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው፣ የምስራቅ ዕዝ አዛዥ ሌ/ጀ መሃመድ ተሰማ እና የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌ/ጀ ብርሀኑ በቀለ ተገኝተዋል።

አቶ ደሳለኝ ጣሰው በዚህ ወቅት÷ የተሃድሶ ሰልጣኞች ውግንናችሁን ለህገ-መንግስቱ እና ለህዝብ መሆኑን አምናችሁና ተቀብላችሁ ስለመጣችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ሌ/ጀ ብርሀኑ በቀለ በበኩላቸው÷ ሀገርና ህዝብን ለመካስ ዳግመኛ ያገኛችሁትን ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ለሀገራችሁ ዘብ መቆም አለባችሁ ሲሉ አሳስበዋል፡፡

የተሃድሶ ሰልጣኞች የክልሉን ህዝብ እንዲሁም ሀገራቸውን ለመጠበቅ ቃል መግባታቸውንም የአማራ ክልል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.