Fana: At a Speed of Life!

አየርላንድ በኢትዮጵያ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የአየርላንድ አምባሳደር ኒኮላ ብሪና ጋር ተወያይተዋል፡፡

ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በውይይቱ ወቅት እንዳሉት÷ በኢትዮጵያ ሴቶችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡

አምባሳደር ኒኮላ ብሪናን በበኩላቸው÷ የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የአየርላንድ መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የስርዓተ-ፆታ እኩልነት እና ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ላይ የሚሰጠውን ድጋፍ ከሚኒስቴሩ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡

በተመሳሳይ ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እና የዩ ኤን ውማን የኢትዮጵያ ተወካይ ሲል መኩሩቡጋ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

በዚህም በስርዓተ-ፆታ እኩልነት እና ሴቶች ማብቃት ላይ የሚሰሩ ሥራዎችን አጠናክሮ ለመቀጠል የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.