Fana: At a Speed of Life!

ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆናቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ከሁለት ሳምንት በኋላ ለሚሰጠው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ከየካቲት 6 እስከ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና ከ112 ሺህ በላይ ነባርና አዳዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰዒድ መሃመድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።

የፈተና ጥያቄዎች ፣ የኮምፒውተር ፣ ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት መስኮች ልየታን ጨምሮ አብዛኛዎቹ የዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለፁት።

ፈተናው መቀሌ አክሱም እና አዲግራት ዩኒቨርስቲዎችን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥም ነው የገለጹት ።

አክለውም ፥ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ቢያጋጥም ችግር እንዳይፈጠር በሁሉም የፈተና ማስጫ ማዕከላት ጄነሬተር ዝግጁ መደረጉንም አብራርተዋል።

ባለፈው ዓመት በፈተና አሰጣጥ ሂደትያጋጠሙ ችግሮች ዘንድሮ እንዳይደገሙ በቂ ዝግጅት መደረጉን አቶ ሰኢድ ተናግረዋል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

 
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.