Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከካናዳው አቻቸው ጀስቲን ትሩዶ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በሀገራቱ የሁለትዮሽ እና ዘርፈ ብዙ ግንኙነቶች ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

በቀጣይ ሀገራቱ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እና የጋራ ግቦችን ለማሳካት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.