አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)በመላው ሀገሪቱ የኮቪድ 19 ወረርሽን ምክንያት አድርገው የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ እና በገበያው እጥረት እንዲፈጠር የሰሩ ከ64 ሺህ በላይ ህገ ወጥ ነጋዴዎች እርምጃ እንደተወሰደባቸው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል አስታወቁ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ የነበራቸው ሚኒስትሩ ÷ሆን ብለው ገበያው እንዳይረጋጋ እና እጥረት ለመፍጠር ሲሰሩ የነበሩ የሸማች ማህበራት አመራሮችን ጨምሮ ህገ ወጥ ነጋዴዎች ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ብለዋል።