Fana: At a Speed of Life!

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ከነገ ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል

አዲስ አበባ፣የካቲት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ አካባቢ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን ተገለጸ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዳስታወቁት÷የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ በሚወጣው መርሐ ግብር መሰረት ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል።

“የዓድዋ ድል፤ መታሰቢያውም የሁላችንም ነው፤ ኑ ቤታችሁን እና ታሪካችሁን ጎብኙ።” ሲሉም ከንቲባዋ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በትናንትናው እለት ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.