የሀገር ውስጥ ዜና

ለሕዳሴው ግድብ ውሃ ሙሌት የሚሆን 1 ሺህ ሄክታር መሬት ምንጣሮ በቀጣይ ሳምንት ይጀመራል

By Tibebu Kebede

June 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት የሚሆን 1 ሺህ ሄክታር የመሬት ምንጣሮ ስራ በመጪው ሳምንት እንደሚጀመር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አስታወቀ።

ለምንጣሮ ስራው 300 ወጣቶች በጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት መደራጀታቸውም ታውቋል።