epaselect epa08356511 View of the funeral service for Natalina Cardoso Bandeira, 68, victim of the COVID-19 pandemic, at the Parque Taruma graveyard, in Manaus, Amazonas, Brazil, 10 April 2020. EPA-EFE/RAPHAEL ALVES

ዓለምአቀፋዊ ዜና

በብራዚል በኮሮና ቫይረስ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከጣልያን በልጧል

By Tibebu Kebede

June 05, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በብራዚል በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 34 ሺህ መድረሱ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎም በሃገሪቱ በኮቪድ19 ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከአውሮፓዊቷ ጣሊያን መብለጡ ነው የተነገረው።

እስካሁን ባለው ሂደትም ከአሜሪካ እና ብሪታንያ ቀጥሎ በርካታ ሰዎች በኮቪድ19 ምክንያት ለህልፈት የተዳረጉባት ሃገር ሆናለች።

ከዚህ ባለፈም በሃገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 580 ሺህ ደርሷል ነው የተባለው።

ፕሬዚዳንት ቦልሶናሮ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ይሰጡት የነበረውን አስተያየትና ሃሳብ ማቆማቸውም ነው የተገለጸው።

ምንጭ፦ ቢቢሲ