Fana: At a Speed of Life!

ባለፉት 5 ዓመታት የተካሄዱ የአዲስ ወግ ውይይቶችን የሰነደ “የአዲስ ወግ መድረኮች” መጽሐፍ ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አምስት ዓመታት የተካሄዱ የአዲስ ወግ ውይይቶችን የሰነደ “የአዲስ ወግ መድረኮች” መጽሐፍ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡

በመርሐ-ግብሩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ ቢልለኔ ስዩም÷ ከርዕሰ ጉዳይ መረጣና አሳታፊነት አንጻር የመድረኩን የአምስት ዓመት ጉዞ ቃኝተዋል፡፡

የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ አዲስ ወግ ለፖሊሲ ግብዓት ሆኖ ማገልገሉን ጠቁመዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሚኒስትር ዲያቆን ዳንኤል ክብረት÷ አዲስ ወግ ቀጣይነት ያለው የውይይት ባህልን ያዳበረ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የታሪክ ምሁሩ ታምራት ሃይሌ (ዶ/ር)÷ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ውይይት ታሪክ ዳስሰዋል፡፡

ጋዜጠኛ ዳዊት መስፍን አዲስ ወግ በመገናኛ ብዙኃን የተሰጠውን ሽፋን የተመለከተ ጥናታዊ ዳሰሳ ማቅርቡን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ቋሚ ዘጋቢዎችም መድረኩን በመዘገብ የነበራቸውን ልምድ አካፍለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.