Fana: At a Speed of Life!

አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 4 ልጆችን ተገላገለች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤንች ሸኮ ዞን ኮሰኮል ቀበሌ ነዋሪ የሆነች አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ሕጻናትን ተገላገለች፡፡
ከአራቱ ሦስቱ ወንዶች መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡

ሕጻናቱ በሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል የእናቶችና ጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም ተገልጿል፡፡

እያንዳንዳቸውም ከ1 ነጥብ 3 እስከ 1 ነጥብ 7 ኪሎ ግራም እንደሚመዝኑ ተጠቅሷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.