የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ተወያዩ

By Feven Bishaw

June 05, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የመተከልና አካባቢው ኮማንድ ፖስት አፈጻጸምን በተመለከተ በባሕር ዳር ተወያይተዋል።

አፈጻጸሙ የተገመገመው የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን በተገኙበት ነው።