Fana: At a Speed of Life!

የዓድዋ ድል በዓል በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች በድምቀት ተከበረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 128ኛው የዓድዋ ድል በዓል በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች በድምቀት ተከበረ፡፡

በዓሉ አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በአማራ፣ አፋር፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ እና ሌሎች ክልሎች በድምቀት ተከብሯል፡፡

በአከባበሩ ላይም የየአካባቢዎቹ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች፣ ዓርበኞች፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ አካላት እና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡

በዓሉ የተከበረው “ዓድዋ የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት” በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.