የሀገር ውስጥ ዜና

ፊንላንድ ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ ማስፈጸሚያ የሚውል የ800 ሺህ ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመች

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 29 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ፊንላንድ ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ ማስፈጸሚያ የሚውል የ800 ሺህ ዩሮ የድጋፍ ስምምነት ተፈራረመች።

የድጋፍ ስምምነቱን በኢትዮጵያ የፊንላንድ አምባሳደር ሄሌና ኤራክሲነን እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት ተወካይ ቱርሃን ሳልህ ተፈራርመውታል።