የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የከተማዋን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት ያስችላል ያለውን ውሳኔ አሳለፈ

By Tibebu Kebede

June 06, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 29 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ።

የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የከተማ መሬት ይዞታ ሊዝ ክፍያ ውዝፍ ዕዳ ማቅለያ እንዲሁም የአልሚዎች የግንባታ መጀመረያና መጨረሻ ጊዜን አሥመልክቶ የተለያዩ ውሣኔዎችን አሳልፏል፡፡