የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

By ዮሐንስ ደርበው

March 12, 2024

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተውጣጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባቶች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለጎብኝዎቹ ገለጻ አድርገዋል፡፡

ጎብኝዎቹም÷ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ታሪኩን፣ ጀግንነቱን እና ጽናቱን በሚመጥን መልኩ ታሪክን ያሸጋገረ፣ ትውልድ የሚማርበት እና በወቅቱ የነበረውን አንድነት በሚገልጽ መልኩ መገንባቱ እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል፡፡