ዓለምአቀፋዊ ዜና

15 ሰዎችን ጭኖ የነበረ የሩሲያ ወታደራዊ አውሮፕላን ተከሰከሰ

By Amele Demsew

March 12, 2024

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 15 ሰዎችን ጭኖ የነበረ የሩሲያ ወታደራዊ መጓጓዣ አውሮፕላን መከስከሱ ተነገረ።

አውሮፕላኑ ከሞስኮ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ በኢቫኖቫ ክልል አየር ላይ እያለ በእሳት ከተያያዘ በኋላ የመከስከስ አደጋ እንዳጋጠመው ተገልጿል።

አይኤል-76 የተሰኘው አውሮፕላን በውስጡ ስምንት የበረራ ሰራተኞችና ሰባት ተጓዦችን ይዞ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን÷ አንደኛው የሞተር ክፍሉ በእሳት ተያይዞና ከባድ የሆነ ጥቁር ጭስ ማውጣቱ በማህበራዊ ሚዲያ የወጡ ምስሎች አመላክተዋል።

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አደጋው ማጋጠሙን ያረጋገጠ ቢሆንም ስለደረሰው ጉዳት ያለው ነገር አለመኖሩን ዲፌንስ ብሎግ ዘግቧል።