Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ኦልድ ቼክ ኤል ጋዙዋን የተላከላቸውን መልዕክት ተቀበሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና የትብብር ሚኒስትር ሞሃመድ ሳሌም ኦልድ ሜርዙግ (ዶ/ር) ጋር በጽሕፈት ቤታቸው መወያየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህ ወቅትም ከሞሪታንያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ኦልድ ቼክ ኤል ጋዙዋን የተላከላቸውን መልዕክት መቀበላቸውን ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.