Fana: At a Speed of Life!

አቶ አሻድሊ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በወቅታዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አሻድሊ ሃሰን ገለጹ፡፡

በውይይታቸውም በሕዝቡ ሠላም እና ደኅንነት ብሎም በልማትና በምርጫ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አቶ አሻድሊ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ባደረግነው ምክክር መሠረትም የቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀምጠናል ነው ያሉት፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.