Fana: At a Speed of Life!

የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ለአብርሆት ቤተ -መጻሕፍት  2 ሺህ መጻሕፍት  አበረከተ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት  የተለያየ ይዘት ያላቸውን 2 ሺህ መጻሕፍትን አበርክቷል።

ኮሌጁን በመወከል መጻሕፍቱን ያበረከቱት የኮሌጁ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ልዑል ከበደ÷ የተበረከቱት መጻሕፍት  ቤተ-መጻሕፉ በንባብ ልምዱ የበለፀገና በዕውቀት የታገዘ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት ያግዛሉ ብለዋል፡፡

ኮሌጁ የንባብ ባህሉ የዳበረ ሀገር ተረካቢ ትውልድ በማፍራት ላይ ለሚገኘው የአብርሆት ቤተ -መጻሕፍት  የሚያደርገውም ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አዛዡ አረጋግጠዋል።

የአብርሆት ቤተ -መጻሕፍት   ቴክኒክ ቡድን አስተባባሪ አቶ ደርብ እርገጥ ኮሌጁ ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.