የሀገር ውስጥ ዜና

የህዳሴ ግድብ በሱዳን እና ግብፅ ከሚገኙ ግድቦች የተሻለ ድህንነት አለው- የሱዳን የመስኖና ውሃ ሚኒስትር

By Tibebu Kebede

June 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በቅርቡ የውሃ ሙሌቱ የሚጀምረው የታላቁ የህዳሴ ግድብ በሱዳን እና ግብፅ ከሚገኙ ግድቦች የተሻለ ደህንነት እንዳለው የሱዳን የመስኖና ውሃ ሚኒስትር ያሲር አባስ ገለፁ።

ሚኒስትሩ ግድቡ ያረፈበት ስፍራ ለሱዳን ካለው ቅርበት ጠቀሜታ እንዳለውም አንስተዋል።