የሀገር ውስጥ ዜና

በዋሽንግተን ዲሲ ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ተጠናቀቀ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ህዳር 30፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዩናይትድ ስቴትስ ዋሽንግተን ዲሲ ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ተጠናቀቀ።

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ አተኩሮ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የሀገራቱ የውሃ ሚኒስትሮችም የተካፈሉ ሲሆን፥ የአሜሪካ መንግስት እና የዓለም ባንክ ተወካዮችም በታዛቢነት ተሳትፍዋል።