Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል  ሆነው ተሾሙ።

አምባሳደሩ  በድጋሚ ቃል አቀባይ ሆነው መሾማቸውን  ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት  ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

በቅርቡም በግብጽ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ሲሰሩ ነበር።

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በተለያዩ ሀገራት በአምባሳደርነት ከማገልገላቸው በፊትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሆነው ማገልገላቸው ይታወሳል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.