የሀገር ውስጥ ዜና

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ለ658 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

By ዮሐንስ ደርበው

April 17, 2024

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ለ658 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው አስታወቁ፡፡

ይቅርታው የተደረገውም ባለፈው ሣምንት የተከበረውን 1ሺህ 445ኛውን ዒድ አል ፈጥር እና መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ መሆኑን ነው ርዕሰ መሥተዳድሩ ያስታወቁት፡፡