አዲስ አበባ፣ ህዳር 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ሰላም እንደ ዛፍ ችግኝ ነው፤ ችግኝን ተክሎ ለማሳደግ ለማሳደግ እንክብካቤ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ሰላምም ጥሩ ልብ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል” አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በኖርዌይ ኦስሎ ዛሬ በተከናወነው የኖቤል የሰላም ሽልማት አሰጣጥ ስነ ስርዓት ላይ ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ በሰላም ዙሪያ ንግግርና ገለፃ አድርገዋል።