Fana: At a Speed of Life!

1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶስት ዙር በረራ በተከናወነ በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ሥራ 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ከተመላሾች ውስጥ 1 ሺህ 98 ወንዶች፣ 79 ሴቶች፣ 3 ጨቅላ ህፃናት  እንዲሁም 228  እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተጠቅሷል።

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.