የሀገር ውስጥ ዜና

ለሰላም ኖቤል ተሸላሚ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ነገ አቀባበል ስነ ስርዓት ይደረጋል

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም የሰላም የኖቤል ተሸላሚ ለሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በነገው እለት የአቀባበል ስነ ስርዓት እንደሚደረግ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በትናንትናው እለት በኖርዌይ ኦስሎ ተገኝተው የዓለም የሰላም የኖቤል ሽልማታቸውን መቀበላቸው ይታወሳል።