Fana: At a Speed of Life!

ሶማሌ ክልል 362 ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች በብድር ሊሰጥ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ግብርና እና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ለአርሶ አደሮች በብድር የሚሰጣቸውን 362 በላይ ትራክተሮች ጅግጅጋ ማስገባቱን አስታወቀ፡፡

ይህም ቢሮው ላለፉት አራት ዓመታት ሲያካሂድ የቆየው የግብርና ምርትና ምርታማነት የማሳደግ መርሐ-ግብር አካል ነው ተብሏል፡፡

ዘመናዊ ትራክተሮችን በብድር የሚወስዱ አርሶ አደሮች 50 በመቶ ቅድሚያ የሚከፍሉ ሲሆን÷ ቀሪውን 50 በመቶ ደግሞ በሁለት ዓመት ውስጥ እንደሚከፍሉ ተገልጿል፡፡

ህብረተሰቡ በብድር የሚጠቀምባቸው ትራክተሮች ክልሉ ምርትን ለማሳደግና በምግብ እራስን ለመቻል ለሚያደርገው ጥረትን ትልቅ ሚና እንዳላቸውም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.