አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የክልሎችንና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አሰራር፣አደረጃጀትና፣አፈፃፀም ምን እንደሚመስል በመዳሰስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጥና ተመሳሳይ የሆነ የይቅርታ አሰጣጥ ስርዓት እንዲኖር የሚያስችል ጥናት ማካሄዱን አስታወቀ፡፡
በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የይቅርታ ቦርድ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዘለቀ ደላሎ እንደገለፁት ፥በ2011 ዓ.ም በነበረዉ ሀገር አቀፍ የጋራ መድረክ ላይ የታራሚዎች የይቅርታ አሰጣጥ ስርዓቱ እንደየ ክልሎች ነባራዊ ሁኔታ የተለየ አሰራርና አፈፃፀም መኖሩ ችግር እየፈጠረ መሆኑ ታምኖበት ሀገር አቀፍ ወጥና ተመሳሳይ የይቅርታ አሰጣጥ ስርዓት ሊኖር እንደሚገባ በመታመኑ ጥናቱ እንደተካሄደ ገልፀዋል፡፡