የሀገር ውስጥ ዜና

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ በውጭ አገር ለሚኖሩ ዜጎች ድጋፍ በሚደረግበት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

By Tibebu Kebede

June 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ድጋፍ በሚደረግበት ዙሪያ በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2012 ዓም ውይይት ተደርጓል።

ውይይቱን በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ የተመራ ሲሆን፤ በውይይቱ የሰላም ሚኒስትር ደኤታ ፍሬአለም ሽባባው፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ፣ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ጆሃን ቦርግስታም፣ የተ.መ.ድ ኤጀንሲዎች በኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶ/ር ካትሪን ሶዚ እና የአለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ማውሪን አቼንግ ተሳትፈዋል።