የሀገር ውስጥ ዜና

የሀብት ምዝበራዎችና ኢ-ሰብዓዊ ጥሰቶች በሚዲያ በመቅረባቸው የተከፉት የተግባሩ ተሳታፊዎች ናቸው- አቶ ንጉሱ ጥላሁን

By Feven Bishaw

June 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ሲፈጸሙ የነበሩ የሀብት ምዝበራዎች በመገናኛ ብዙሃን በመቅረባቸው የተከፉት የተግባሩ ዋነኛ ተሳታፊዎች መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናገሩ።

አቶ ንጉሱ የሃብት ምዝበራ ተዋንያኖች ብሔርን እንደ ዋነኛ መደበቂያ ምሽግ እየተጠቀሙበት መሆኑንም ነው የገለጹት።