የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ በወሊሶ ከተማ የኦሮሚያ ክልል የዜግነት አገልግሎትን በይፋ አስጀመሩ

By Tibebu Kebede

June 13, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በወሊሶ ከተማ ተገኝተው የኦሮሚያ ክልል የዜግነት አገልግሎትን በይፋ አስጀመሩ።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።