የሀገር ውስጥ ዜና

በህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ በእስያ ሀገራት ዘንድ ግልጽነት እንዲፈጠር ተሰርቷል- በኢንዶኔዥያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ በእስያ ሀገራት ዘንድ ግልጽነት እንዲፈጠር መሰራቱን በኢንዶኔዥያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።

በኢንዶኔዥያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶክተር አድማሱ ጸጋዬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት፥ የእስያ አባል ሀገራት ኢትዮጵያ በቀጠናው እየፈጠረች ያለውን ትስስር ለመደገፍ ዝግጁነት ማሳየት ጀምረዋል።