የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በኢትዮጵያ የ10 ዓመት የልማት መሪ ፕላን ረቂቅ ላይ እየተወያየ ነው

By Tibebu Kebede

June 13, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኢትዮጵያ የ10 ዓመት የልማት መሪ ፕላን ረቂቅ ዙሪያ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

የ10 ዓመት እቅዱ እስከ 2022 ዓ.ም ለመከናወን የታቀደ ሲሆን፥ የፖሊሲና ስትራቴጂ ፣ ያለፉት አመታት አፈጻጸምና የዓለም አቀፍና ከባቢያዊ ሁኔታዎችን እንዲሁም ግቦችን መሠረት በማድረግ የታቀደ ነው።