አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በመሆን በዛሬው እለት ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር አካሂደዋል።
የብልጽግና ፓርቲ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ)፣ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራት ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ)፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) እና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት በየካ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የሚሌኒየም ፓርክ ችግኝ ተክለዋል።