አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀረሪ ክልል ኮሮና ቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ተናገሩ።
በሚኒስትር ዲኤታው የተመራው የልዑካን ቡድን በሀረሪ ክልል ተገኝቶ ኮቪድ-19ን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የተቋቋሙ አምስት የተለያዩ የለይቶ ማቆያና ህክምና መስጫ ማዕከላት እንዲሁም ሁለት የላቦራቶሪ ምርመራ ማዕከላትን ጎብኝቷል።