የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከጅቡቲ የንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው የልዑካን ቡድን ከጅቡቲ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የሱፍ ሙሳ ደዋሌና ከንግድ ምክር ቤቱ አባላት ጋር ተወያየ።

አቶ ሽመልስ ሁለቱ ሃገራት ካላቸው ጥብቅ የንግድና የቢዝነስ ትስስር አንጻር የኦሮሚያ ክልል የቢዝነስ ማህበረሰብ በዚህ ሰፊ ዕድል በንቃት በመሳተፍ ግንኙነቱን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል።