አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ መካከል በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚካሄደው ድርድር ትናንትም ቀጥሎ ውሏል።
የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ድርድሩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፥ በትናንትናው ስብሰባ ሶስቱ ሀገራት በህዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና ዓመታዊ የስራ ክንውን ጋር በተያያዘ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው መደራደራቸውን ሚኒስቴሩ አስታውቅዋል።