የሀገር ውስጥ ዜና

የሚዲያና ኪነጥበብ ባለሙያዎች የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከሉ ሥራ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገለፁ

By Tibebu Kebede

June 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሚዲያና ኪነጥበብ ባለሙያዎች የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከሉ ሥራ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የፕረስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገለፁ።

ዛሬ የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የስራ ሀላፊዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ያሉበት ብሄራዊ የሚዲያና ኪነጥበባት ግብረኃይል፣ የጤና፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴሮች የስራ ሀላፊዎች የተገኙበት ቡድን በቦሌ ሚካኤል አካባቢ የችግኝ ተከላ በማከናወን ላይ ይገኛል።