አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለም ዙሪያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ8 ሚሊየን መሻገሩ ተገለፀ።
የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ እንደሚያመለክተው በአሁኑ ወቅት በዓለም ዙሪያ 8 ሚሊየን 34 ሺህ 461 የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን 3 ሚሊየን 875 ሺህ 339 ሰዎች ከቫይረሱ ሲያገግሙ፤ 436 ሺህ 901 ሰዎች ደግሞ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል።