የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ድጋሚ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደው ድጋሚ ምርጫ ድምጽ የተሰጠባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ነው።
በክልሉ ምሥራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ እና በማረቆ ልዩ ወረዳ 6ኛው ሀገራዊ የድጋሚ ምርጫ ላይ ዜጎች በትናንትናው ዕለት ድምጻቸውን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡
በምርጫው ሒደት ሲሳተፉ የነበሩ መራጮችም በዛሬው ዕለት የተለጠፈውን ጊዜያዊ ውጤት እየተመለከቱ ይገኛሉ።
የድጋሚ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ በአካባቢዎቹ በሚገኙ በ169 የምርጫ ጣቢያዎች መከናወኑ ይታወቃል።
በይስማው አደራው